የተመሰረተው 1954 በግርማዊ ነጉሠ ነገስት በአፄ ሐይለሥላሴ ነው ቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ከዘመነ መሳፍት እስከ አፄ ሐይለ ሰላሴ ድረስ አንድ ነበሩ ነገስታቱ ሁሉ ሀይማኖተኛ እና ቀናተኛ ነበሩ በተለይ ሁሉ ህገ እግዚአብሔርን ጠብቀው የሚያስጠብቁ ነበሩ ለቤተክርስቲያን ታላቅ ውለታ የሚውሉ ነበሩ በተ ክርስቲያን በማሳነፅ መፅሐፍ በመፃፍ ቅዱሳት መፅሐፍትን በመከባከብ በማስደጎስ ቅርስን ጠብቆ በማስተበቅ የሐይማኖት ሕፀፅ ያለባቸውን መነፍቅ ሊቃውንት ተሰብስበው መልስ እንዲሰጡና እንክርዱዱን እንዲለዩ ቦታና ጊዜ በማመቻቸት በአሕዛብ ነገሥታት የተወሰደባትን መብት በመመለስ እና ባለ ሙሉ መብት ያላት በማድረግ ነገሥታቶች ለቤተክርስቲያን የዋሉት ውለታ ትውልድ አይመልሰውም ነገሥቱ ቤተክርስቲያን እራሷን እንድትችል ከቤተመንግሥት እንኳን በንጉስ ቆስጠንጢኖስ ዘመን ግብር ይከፈላት ነበር ቤተክርስቲያን የነስጋና የነፈስ ባለመዳህኒት የጥበብ መህደር እንደመሆኗ መጠን አድሎ በሌለበት በእግዚአብሔር ሕገ ይመሩ ነበር ይህም እስከ አፄ ሐይለ ስላሴ ድረስ ነው ከአፄ ሐይለ ስላሴ ወዲህ ነገሥታትና ቤተክርስቲያን እየተራራቁ መጡ በተላይ ቤተክርስቲያን በፍትሕ መንፈሳዊ እና በፍትሐ ነገሥት የታወቀች ስትሆን ነገሥታቶች ሁሉ በዚህ አልፈዋል አፄ ሐይለ ሥላሴ 19954 ገዳሙን ሲመሰሩቱ የነበረው የቦታው ሁኔታ ሰው የሌለው ጫካ በርሃ ነበር የሰው መጠንም ትንሽ ነበር ከግዜ ወዲህ ግን ከተማው እየሰፋ ክርስቲያን ስደተኞች እበዙ ዳር የነበረው አሁን መሐል ሁኖል ገዳሙ ከሐገር ለሚሰደዱት ሰደተኞች መጠለያ በመሆን ብዙ አመታትን አስቆጥሯል ገዳሙ በወቅቱ ጠባብ እና መንፍሳዊ አገልግሎቱም ትንሽ ነበር አሁን ግን በስደት የተወለዱትም ተሰደው የመጡት እየበዙ አገልግሎቱ እየሰፋ ሂዷል ገዳሙን በተለያየ ዘመንና ጊዜ ብዙ ካህናት አባቶቻችን አስተዳድረውታል ይልቁንም ገዳሙ ከተመስረተበት 1954 ዓ፡ም ጊዜ ጀምሮ እስከ 1983 ዓ፡ም የአገልግሎት እና የገቢ እጥረት ነበረው በተላይ በቂ ካህናት እና ዲያቆናት አለመኖር ይልቁንም ዛሬ ለቤተክርስቲያን የጀርባ እጥንት በመሆን አገልገሎት እየሰጠያለው የወጣቶች ህብርት ሰንበት ት/ቤት አለመኖር ገዳሙ ላለመስፈቱ ምክኒያት ሆኖ ነበር በእግዚአብሔር ፈቃድ በብፁዕ ወቅዱስ አቡ ቴዎፍሎስ ቅዱስ ሐሳብ 1965 በሰረት የያዘው ሰንበት ትምህርት ቤት